(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂዋ አርቲስት ሜሮን ጌትነት በሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ የልጅ እናት ለመሆን መብቃቷን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመከተ::
ሜሮን ጌትነት ከዳና ድራማ ላይ የተቀየረች መሆኑን እና ኑሮዋም አሜሪካ እንደሆነ ዘ-ሐበሻ ቀደም ብላ ጽፋ የነበረ መሆኑ ይታወቃል::
ሜሮን ባለፉት 2 ሳምንታት ውስጥ 2 ጊዜ የልጅ እናት ትሆናለች በሚል ሆስፒታል ስትመላለስ መቆየቷን የጠቆሙት የዘ-ሐበሻ ምንጮች ትናንት ማምሻውን ወደ ኢመርጀንሲ ክፍል ተወስዳ የሴት ልጅ በሰላም ተገላግላለች::
ዘ-ሐበሻ ሜሮንን እንኳን ደስ ያለሽ ትላለች::
The post ሜሮን ጌትነት በሚኒሶታ የልጅ እናት ሆነች appeared first on Zehabesha Amharic.