Quantcast
Viewing all articles
Browse latest Browse all 261

ፍልፍሉ በአዲስ አበባ ክፉኛ ተደበደበ

(ዘ-ሐበሻ) በረከት በቀለ ወይም በገጸ ባህሪይ ስሙ “ፍልፍሉ” በሚል የሚታወቀው ኮሜዲያን ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ለሥራ ከተመለሰ በኋላ በአዲስ አበባ ከፍተኛ ድብደባ እንዳጋጠመው የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ ዘግበዋል።
Image may be NSFW.
Clik here to view.
filfilu

ኮሜዲያኑ በሰሜን አሜሪካ በተለያዩ ከተሞች እንዲሁም በ እስራኤል ሃገር የኮሜዲ ሥራዎቹን አቅርቦ በቅርብ የተመለሰ ሲሆን ከ2 ቀናት በፊት ድብደባ የተፈጸመበት በፒያሳ አካባቢ መሆኑን ዘጋቢዎቻችን ገልጸዋል። ኮሜዲያኑ ወደ ፒያሳ የሄደው ከባለቤቱ እና ከባለቤቱ እህት ጋር እንደነበር የገለጹት ዘጋቢዎቻችን ፊቱ ላይ ጭምር ሳይቀር ድብደባ ፈጽመውበት ጥርሱ ሌላኛው ጥርሱ መውለቁንም ገልጸዋል።

በፍልፍሉ ላይ ጥቃት ያደረሱት ሰዎች እነማን ይሁኑ የታወቀ ባይሆንም ኮሜዲያኑ ለፖሊስ ከህክምና ካገገመ በኋላ ቃሉን መስጠቱ ታውቋል። እነዚህ ዘራፊዎች ምናልባትም በኮሜዲያኑ ድብደባ የፈጸሙት በቅርቡ ከአሜሪካ በመመለሱ ገንዘብ ይዞ ይሆናል በሚል ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ኮሜዲያኑ በቅርቡ ከሰይፉ ፋንታሁን ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ “ክበበው ከአሜሪካ ሲመለስ ቤት ሲገዛ፤ እኔ ግን አደብ ገዝቼ ተመለስኩ” ሲል ገንዘብ እንዳልያዘ በቀልድ መናገሩ አይዘነጋም።

ፍልፍሉ በሰሜን አሜሪካ ቆይታው ያልፈረምኩበትና፤ ያልተከፈለኝ ሲዲ በስሜ ወጥቷል ሲል ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቀው በዘ-ሐበሻ በኩል አስተላልፎት የነበረው ቪዲዮን ለግንዛቤ ይመልከቱት።

በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ላይ የፍልፍሉ እና የቁልሉ ጨዋታ በሚል የቀረበውን ቃለምልልስ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


Viewing all articles
Browse latest Browse all 261

Trending Articles