“ስለ ፍቅር ሲባል ስለ ጸብ ካወራን ተሣስተናል”
- አርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን
ከአስተባባሪው ኮሚቴ፦
በዓለም ዋንጫ እንዲገኝ ኢትዮጵያን እና አፍሪካን ወክሎ ለተመረጠው ኢትዮጵያዊ አርቲስት ድጋፋችንን እንግለጽለት የሚል ነው። መልእክቱ ቴዲ አፍሮን ለመደገፍ ብቻ እንደተፃፈ አትመልከቱት። ከዚህ በላይ ሰፋ አድርጋችሁ ለአገራችንን ውክልና ድጋፍ ለመስጠት እንደተፃፈ አስቡት። ተመርጦ የነበረው አርቲስት አሊ ቢራም ቢሆን አለያም አስፋው ጀብጀብ፤ መልእክታችን የሚሆነው ይኸው ነበር። አርቲስቱ ማንም ይሁን ማን፣ አገራችን ያገኘችው ይህ ወርቃማ ዕድል በስኬት እንዲጠናቀቅ እጅ ለእጅ እንያያዝ ነው እያልን ያለነው። በቃ። ከዚህ ውጪ ምንም ትርጉም የለውም። ዋነኛ የቆምንለት ዓላማ ፍቅርንና ወንድማማችነትን ማወጅ ነው።
ለቴዲ ድጋፍዎን ለመግለጽ የሚከተለውን የፌስቡክ ገጽ ላይክ ያድርጉ https://www.facebook.com/pages/Teddy-Afro-to-represent-Africa-for-2014-FIFA-Coca-Cola-world-cup/217835185067743
የቴዲ የብራዚል ጉዞ – ድጋፍዎን በፌስ ቡክ ይግለጹ:
ይህንን ፔጅ ይውደዱ >> Like the page Teddy Afro to represent Africa for 2014 FIFA world cup