‘ሳላይሽ’ የተሰኘ ተወዳጅ አልበሙን ለሕዝብ ካቀረበ በኋላ ከፍተኛ ተቀባይነትን በማግኘቱ በየሃገራቱ እየተዘዋወረ የሙዚቃ ኮንሰርቶቹን በማቅረብ ላይ ያለው ድምፃዊ ብዙአየሁ ደምሴ በካናዳ ዊኒፔግ ግዛት ከትናንት በስቲያ ሴፕቴበር 6 አምርቶ ነበር:: ኮንሰርቱን ለመሥራት ወደዚያው ያመራው ይኸው ተወዳጅ ድምፃዊ በአንድ ወጣት በተወረወረ ጠርሙስ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል ገብቶ እንደነበር ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል::
በጠርሙስ ፍንከታ የደረሰበት አካሉ መሰፋቱን የገለጹልን ምንጮቻችንን ጠርሙሱን የወረወረበትን ሰው ለመያዝ ፖሊስ እየጣረ መሆኑም ተሰምቷል::
ብዙአየሁ በዌኒፒግ ኮንሰርት ሊያቀርብ ሲሄድ የም ዕራብ ካናዳ የኢትዮጵያውያን እግር ኳስ ውድድር ይካሄድ እንደነበር ታውቋል::
ዘ-ሐበሻ ወደ ብዙአየሁ ደምሴ ደውላ ጉዳዩን ከ እርሱ አፍ ለመስማት ያደረገችው ሙከራ ባይሳካም ከርሱ እንደሰማን የምናቀርብ መሆናችንን እንገልጻለን::
ኢትዮጵያውያን በውጭ ሃገር ኮንሰርት ለማየት ሄደው በኮንሰርት ላይ መደባደብን እንደ ትልቅ ጀብዱ ማየታቸው የሚያሳዝን ጉዳይ ሲሆን; ይህን ዓይነቱን ድብድብ የሚፈጥሩት ደግሞ የራሳቸው ወገን ባዘጋጀው ኮንሰርት ላይ እንጂ በውጭ ሃገር ኮንሰርቶች ላይ አለመሆኑ ብዙዎችን ያሳዘነ ጉዳይ ነው::